ኦሮሚያ ባንክ የስኬት ጎዳና ላይ ይገኛል
ኦሮሚያ ባንክ በሁሉም የአፈፃፀም መመዘኛዎች የዕድገት ጎዳና ላይ እየተጓዘ ይገኛል፡፡
ባንካችን 12ኛውን የባለ አክሲዮኖች ዓመታዊ ጠቅላላ ጉባዔን ቅዳሜ ታህሳስ 16 ቀን 2014 ዓ.ም ያካሄደ ሲሆን በቀረበዉ የዳይሬክተሮች ቦርድ ሪፖርት ላይ እድገቱ ቀርቧል፡፡
በዚህም መሠረት የባንካችን ጠቅላላ ሀብት በ23% ጨምሮ ብር 41.7 ቢልዮን ደርሷል፤ በተጨማሪም የባንካችን የደንበኞች ብዛት ከቀዳሚው ዓመት ጋር ሲነጻጸር በ45 ከመቶ በመጨመር 2.49 ሚሊዮን የደረሰ ሲሆን፣ የባንኩ ተቀማጭ ገንዘብ በ24 ከመቶ በመጨመር 34.35 ቢልዮን ደርሷል፡፡
ባንካችን በመደበኛው የባንክ ሥራ የሰጠው ብድር እና ከወለድ ነፃ በሆነው የባንክ ሥራ የሰጠው ፋይናንሲንግ በድምር ከቀዳሚው ዓመት በ27 ከመቶ አድጎ ብር 25.77 ቢልዮን ደርሷል፡፡ከዚሁ አፈጻጸም ጋር ተያይዞ ባንካችን በበጀት ዓመቱ ከግብር በፊት ብር 1.13 ቢሊዮን ትርፍ አስመዝግᎆል፡፡
በሌላ በኩል የባንካችንን ሁለንተናዊ አፈጻፀምና የመፈጸም አቅም በወሳኝ ሁኔታ እንደሚያሻግር የታመነበት የላቀ የደንበኛ አገልገሎት አሰጣጣችንን በእጅጉ የሚያሳልጥ የሦስተኛ ዘመን የአምስት አመት የስትራቴጂ ዕቅድ ተቀርጾ የትግበራ ጅማሮ ላይ ይገኛል። አዲሱ ብራንዳችንም በአዲስ ገጽታ፤ በአዲስ ምልከታና በታደሰ አስተሳሰብ ደንበኞቻችንን የምናገለግልበት የቃልኪዳን ምልክታችን ነዉ፡፡
ለስኬትዎ እንተጋለን!
May be an image of text that says '4,259 Permanent Staff 5% 41.7B Asset 23% 6,418 Total Employment 4.52B Revenue 7% 18% 34.35B Deposit 24% 3.38B Expense 743 Service Outlet 13% 22% 25.77B Loan and Financing IFB 27% 316 Branches 1.13B Profit before tax 6% 5% 6 31B NBE Bill 4% 2.49M Regular Customers 257M Income Tax 45% 181M FCY 26% 21% 632,228 E-channel Customers 872.0M Net Profit 101% 1% 5-49B Total Capital 19% 270 Earnings share 11,760 Borrowers Per 10% 16% 3.46B Paid Up Capital 15% 228 Average dividend per share 34%'